Login    Search   
   Date: 2008-04-18   Volume: 3    Issue: 36
  Sat, September 4, 2010
    This Week
     News
     Commentary
     ABBI Feature
  
   በዚህ ሳምንት
     ዜና
     የስኬት ፈርጦች
     ሳይንስና ቴክኖሎጂ
     ነጥብ
     እንዲህ ቢሆንስ
     አውደ ኪን
     ህግና ማኅበረሰብ

የአፍሪካ መሪዎች ራስ ምታት

ከጌታቸው ንጋቱ
መለስ ለኤርትራ ጉዳይ መቋጫ ይፈልጋሉ

·          ካቢላ የአባታቸው ዙፋን እያቃጠላቸው ነው

·          አዛውንቱና ታማሚው ዩሱፍ አልሆነላቸውም

·          የፀጥታው ምክር ቤት የአፍሪካ ጉዳይ መሮታል

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከሴኔጋል ዳካር  የኔፓድ ስብሰባ በቀጥታ ወደ ኒውዮርክ በማምራት ከፀጥታው ምክር ቤት ጋር በሚደረገው ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል፡፡ በስብሰባው ላይ በአፍሪካ ያሉ የፀጥታ ችግሮች ላይ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ከጥታው ምክር ቤት አባል አገራት መሪዎች ጋር የመከሩ ሲሆን የፀጥታው ምክር ቤት ጊዜውን በአፍሪካ ጉዳይ ላይ ማጥፋት እንደመረረው ገልጿል፡፡

ቴዲ አፍሮን ዘብጥያ ያወረደ የሞት አደጋ

ከዮሐንስ አንበርብር

ዝነኛው አርቲስት ቴድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥር 23 ቀን 1999 ዓ.ም ነበር ከካናዳ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው፡፡ የዚያን ቀን ሌሊት ግን ምናልባትም ለሁለት ሰዎች ክፉ እጣ ነበር፡፡ ለቴዲ አፍሮና ለደጉ ይበልጣል፡፡ ከካናዳ ለመጣው ዝነኛ አርቲስትና በጎዳና ላይ ለሚኖረው ቤተሰብ አልባው ዜጋ፡፡ (ወረዳ 17)  

ጥር 23 ከሌሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ነው በተለምዶ ፊት በር ወይም ሸራተን አካባቢ የአንድ ግለሰብ አስክሬን በፖሊስ ይገኛል፡፡ ይህ ግለሰብ በመኪና ተገጭቶ መሞቱን ለማረጋገጥ ከባድ አልነበረም፡፡ ፈታኙ ነገር ግን ይህንን ግለሰብ ማን ገደለው ወይም ማን ገጨው? የሚለው ጥያቄ ነበር፡፡

ከአወዛጋቢው ዓባይ ገባሮች በአንዱ ግንባታ ተጀመረ

ከዮሐንስ አንበርብር

ግብጽና ሱዳን በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ አስር ዓመታትን የፈጀ ውይይት ከተፋሰስ ሀገራት ጋር ቢያደርጉም ኢትዮጵያ የተፋሰሱን አጠቃቀም አስመልክቶ ባስቀመጠችው ነጥብ ላይ ለመግባባት አልቻሉም፡፡ ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ካቀደቻቸው አምስት የአባይ ገባር ወንዝ ግድብ እቅዶች የአንዱን ግንባታ ጀምራለች፡፡

የኢትዮጵያ የውሃ ሀብት ሚኒስትር የሆኑት አቶ አስፋው ዴንጋሞ ባለፈው ማክሰኞ እለት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባቀረቡት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ስምምነት ሊደረስበት ያልቻለበትን ምክንያት ተናግረዋል፡፡

የኀብረትና ኦፌዴን ሕጋዊነት ሊሰረዝ ይችላል

ከጌታቸው ንጋቱ

በአካባቢና የማሟያ ምርጫ ከመወዳደር ራሳቸውን ያገለሉት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች ኀብረት (ኢዴኃ) እና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ሕጋዊ ሰውነት ሊነሳ እንደሚችል ተጠቆመ፡፡ የሁለቱንም ፓርቲዎች ድርጊት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አወገዘ፡፡

መከላከያ ሚኒስቴርና የእንግሊዝ ኤምባሲ የስልጠና ስምምነት ተፈራረሙ
ከጌታቸው ንጋቱ

የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስቴርና የእንግሊዝ ኤምባሲ በትናንትናው እለት የስልጠና ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ስምምነቱ ለኢትዮጵያ ወታደሮች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት በመስጠት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚደረጉ የሰላም ማስከበር ሥራዎች ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ነው፡፡

የእንግሊዝ ኤምባሲ አምባሳደር ሚስተር ኖርማን ሊንግ እና የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ካሣሁን ደንድር በትናንትናው ዕለት የስምምነቱን የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙ ሲሆን ኢትዮጵያ በውጭ አገራት በሚደረጉ የሰላም ማስከበር ሥራዎች ላይ በስፋት እንድትሳተፍ ያደርጋል ተብሏል፡፡

እነ ኢ/ርን ኃይሉ ምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መሠረቱ

ከጌታቸው ንጋቱ

በኢንጅነር ኃይሉ ሻውል የሚመራው የቀድሞው ቅንጅት ስሙ ለሌላ በመሰጠቱ በምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መሰረተ፡፡

ሚያዚያ 8/2000 ዓ.ም አዲስ አበባ ላለው ከፍተኛው ፍርድ ቤት የደረሰው ክስ እንደሚገልፀው አራቱ የፖለቲካ ድርጅቶች መስከረም 14/1998 ውህደት መፈፀማቸውንና ውህደቱን የፈጸመው የቅንጅት ፓርቲ ሕጋዊ ሰውነት እንዲሰጠው የውህደቱን ሰነድ አያይዞ ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረቡን ገልጾ በአንቀጽ 24 መሠረት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ መስጠት ሲገባው የምዝገባ ጥያቄው የተሟላ ባለመሆኑ ለቦርዱ አይቀርብም ሲል በጽሕፈት ቤት በኩል መልስ መስጠቱ ተገቢ እንዳልነበር ይገልጻል፡፡

የለገዳዲ ውሃ ማጣሪያ የመበከል አደጋ ተጋርጦበታል

ከዮሐንስ አንበርብር

ለአዲስ አበባ ከተማ በቀን 160ሺ ሜትሪክ ኪዩብ የመጠጥ ውሃ እያቀረበ የሚገኘው የለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ግድብ በአካባቢው በሚገኙ አርሶአደሮች የመበከል አደጋ ተጋርጦበታል፡፡

የውሃ ሀብት ሚኒስትሩ  አቶ አስፋው ዴንጋሞ  ባለፈው ማክሰኞ ዕለት ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀማቸውን ባቀረቡበት ወቅት፣ የምክር ቤቱ አባላት በአዲስ አበባ የውሃ ችግር ላይና በተለይም በለገዳዲ የውሃ ማጣሪያ ግድብ ላይ ከፍተኛ የብክለት አደጋ መጋረጡን በራሳቸው መንገድ ለመመልከት እንደቻሉና ባለሙያዎችንም አነጋግረው በአስቸኳይ የዕርምት ርምጃ ካልተወሰደ በአዲስ አበባ ሕዝብ ላይ የጤና ጉዳት እንደሚደርስ የተገለፀላቸው መሆኑን ለሚኒስትሩ አሳስበዋል፡፡

እሁድ ዕለት የታየችው ባለቀለበት ፀሐይ የበረከት ምልክት ተባለች

ከጌታቸው ንጋቱ

ሚያዚያ 5ቀን 2000 ዓ.ም በጠዋት ማልደው ወደ ቤተክርስቲያንና ወደ ምርጫ ጣቢያ የሄዱ ሰዎች የተመለከቷት ፀሐይ ከወትሮው የተለየች ነበረች፡፡ ደርግ በ1983 ዓ.ም ሲወድቅ የታየችው አይነት ፀሀይ መሆኗን ብዙዎች ተናግረዋል፡፡ ፀሀይዋ የእግዚያብሔር ተዓምር መገለጫ ምልክት መሆኗንም የሀይማኖት አባቶች ገልፀዋል፡፡

ፀሀይዋ እስከ ቀትር ድረስ እየደበዘዘች ብትመጣም በቀለበት ታጥራ ረፋዱን ሞቅ ስታደርግ ውላለች፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም ፀሀይዋን ቀና ብለው ባያዩም በዕለቱ የነበረውን የአየር ፀባይ እጅግ አድርገው እንደወደዱትና ዕለቱም የተባረከ ብሩህ ቀን ነው ሲሉ የተደመጡ አሉ፡፡

ዜና
 

የአፍሪካ መሪዎች ራስ ምታት

 

ቴዲ አፍሮን ዘብጥያ ያወረደ የሞት አደጋ

 

ከአወዛጋቢው ዓባይ ገባሮች በአንዱ ግንባታ ተጀመረ

 

የኀብረትና ኦፌዴን ሕጋዊነት ሊሰረዝ ይችላል

 መከላከያ ሚኒስቴርና የእንግሊዝ ኤምባሲ የስልጠና ስምምነት ተፈራረሙ
 

እነ ኢ/ርን ኃይሉ ምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መሠረቱ

 

የለገዳዲ ውሃ ማጣሪያ የመበከል አደጋ ተጋርጦበታል

 

እሁድ ዕለት የታየችው ባለቀለበት ፀሐይ የበረከት ምልክት ተባለች

   ተጨማሪ...
Designed and Developed by ReliIT